ትናንሽ እርምጃዎች

 

   

​ትልቅ ተራራን ለመናድ መጀመሪያ ትናንሽ ድንጋዮችን ማንሳት መጀመር ይኖርብሃል። ዛሬ የምታደርጋት አነስተኛ ጥረት፣ የምትማራት አዲስ ክህሎት ወይም የምትጀምራት ትንሽ ስራ ቀላል ልትመስል ትችላለች። ነገር ግን የነገው ትልቅ ስኬትህ መሠረት እሷው ነች። በሂደቱ ላይ እምነት ይኑርህ፤ ዛሬ የምትዘራው ዘር ነገ ማማሩ አይቀሬ ነው!

​🌱 በትናንሽ ጅምሮች አትፈር፣ ታገስ፣ በየቀኑ ጥቂት እርምጃ ወደፊት ተራመድ።

ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል ሁለት

                              የማይታየው እጅ 


አቶ ታምራት በቢሯቸው መስኮት በኩል የሚያዩትን የከተማዋን ውበት ጥለው ወደ ጠረጴዛቸው

ተመለሱ። በዝግጅት ላይ ያለው የዛሬ ምሽቱ ግብዣ ከፍ ያለ ክብር እንደሚሰጣቸው ያውቃለ። ልክ

ወንበራቸው ሊይ እንዯተቀመጡ ግን ባሌተሇመዯ መሌኩ በቢጫ ፖስታ የታሸገ ዯብዲቤ በጠረጴዛቸው

መሃል ተቀምጦ አዩ።

"ይህንን ማን አምጥቶ እዚህ አስቀመጠው?" ብለው ጮኹ። ረዳታቸው እየተንቀጠቀጠ ገባ። "ጌታዬ... 

እኔ አላየሁም፣ ማንም አልገባም" አላቸው።

ታምራት ደብዳቤውን በቁጣ ቀደዱ። ውስጥ ያለው ግን ጽሐፍ ሳይሆን አንዴ የቆየ ፎቶ ነበር።

ፎቶው የዛሬ ሃያ አመት በፊት የተነሳ ነው። ታምራት እና ሶስት ጓደኞቻቸው ምሽግ በሆነ ሰፈር፣

ፊታቸው ላይ ስጋት እየታየ አንድ ትልቅ ቦርሳ ይዘው ይታያለ። በፎቶው ጀርባ ላይ እንዲህ የሚል

ጽሐፍ በደም ቀለም የሚመስል ቀይ ቀለም ተጽፏል፦

"ስሌጣን ላይ ስትወጣ የረገጥከው መሰላል፣ መውረጃህ ሊይ እሾህ ሆኖ ይጠብቅሃል። ያንን ቦርሳና

በውስጡ የነበረውን ሚስጥር ረሳኸው ታምሬ?"

ታምራት ትንፋሻቸው ተቆረጠ። "ታምሬ" ብሎ የሚጠራቸው ያ የዴሮ ጓደኛቸው መሞቱን እርግጠኛ

ነበሩ። እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስልኩን አነሱ። የደህንነት ክፍሉን በመጥራት አስበው ግን ተዉት። ይህ

ሚስጥር ከወጣ ስልጣናቸው ብቻ ሳይሆን ህይወታቸውም እንደሚያከትም ያውቃሉ።

በዚህ መሃል የቢሮው ስሌክ አቃጨለ። "ሄሎ" አሉ።

ዴምፁ ቀዝቃዛ ነው... "ጣዕሙ እንዴት ነው ታምራት? ገና መራራው ክፍሌ አልደረሰም። ዛሬ ምሽት

ግብዣህ ላይ እገኝ ይሆናል" ብሎ ተዘጋ።

ታምራት ቢሯቸው ውስጥ ብቻቸውን ሆነው ላባቸው ይፈስ ጀመር። ያንቋሸሹት ህዝብ ሳይሆን፣

የቀበሩት ታሪክ አፋቸውን ከፍቶ ሊውጣቸው እንደመጣ ተገነዘቡ......

                                  ይቀጥላል.......

 


ታማኛለች ቀርፋፋ ነው እያለች ፤ አላወቀችም ከብዙ ቀን ጥርቅም በኋላ መራመድ እንደሆነልኝ  ፤ ተዓምር ሆኖ ባርቆብኝ ፣ ደክሞኝ እየተራመድኩ እንደሆነ ብታውቅ መንቀራፈፌ ሳይሆን መራመዴ ትንግርት ይሆንባት ነበር!

ደግሞ  አሮጌ ጨርቅ ማጥለቄ  ደህይቼ  መስሏታል ፤ ከጎዳና ላይ ተነስቼ  ከብጭቅጫቂ ጨርቅ ወደ አሮጌ ጨርቅ ማደጌን ብታውቅ ደህይቼ ሳይሆን እያለፈለኝ መሆኔን ትገነዘብ ነበር።

ትክ ብዬ ማየቴ  ድፍረት ነው የመሰላት ፤ አንገቴን ደፍቼ መኖሬን ብታውቅ ቀና ከማለት አድጌ በልበ-ሙሉነት ማየቴ ድፍረት ሳይሆን ልበ-ሙሉነቴ አድጎ እንደሆነ ትመሰክርልኝ ነበር ። 

እግረመንገዱን የመጣ መዛኝ እየመዘነ ነው የሚያስቀን !

ችላ ስትለኝ ችላ ማለቷን ከቁብ ያለመቁጠር  ንቀት  ነው የመሰላት  ግን አይደለም ፤
የስህተታችን ጅማሬ በሁሉም ሰው ተቀባይነት ለማግኘት መዳከር ነው የሚለው ጥበብ ገብቶኝ እንጂ ። 

እኔ ግን ትግሌ ከራሴ ትናንት ጋ ነው!!!
              
@keye_ber

ስልጣንና ጣዕሙ


         ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል አንድ 

አቶ ታምራት ጥቁር መስታወት ባለው ዘመናዊ መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመስኮት ወደ ውጭ

ይመለከታለ። መንገደ በሰዎች ብዛት ተጨናንቋል። ፀሃዩ የበረታበትና ላባቸውን በክንዳቸው የሚጠረጉ

ሰራተኞች፣ ቅርጫት የተሸከሙ እናቶች፣ እና አቧራ የለበሱ ህፃናት በመንገደ ግራና ቀኝ

ይተማመታሉ።

ታምራት ፊታቸውን አኮሳተሩ። "ይህ ሁለ ህዝብ የት ነው የሚሄደው? መንገደን እንዱህ

የሚያጨናንቁት ስራ ስለሌላቸው ነው" አለ። አብሯቸው የነበረው የግሌ ረዲታቸው። ዴምፃቸው ውስጥ

ከፍተኛ ንቀት ይንጸባረቃል። ከጥቂት አመታት በፊት ምርጫ ሲቃረብ፣ በእነዚሁ ሰዎች ሰፈር እየተገኙ

"እኔ የእናንተ ሌጅ ነኝ፣ ለውጥ አመጣለሁ" እያለ ጎንበስ ብልው ሲማጸኑ የነበሩት ታምራት፣ ዛሬ

በህዝቡ መሀል ማለፍ እንደ መርገም ቆጥረውታል።

ለእሳቸው ህዝብ ማለት ስልጣን ሊይ እስኪወጡ የሚጠቀሙበት "ቁጥር" ብቻ ነው። አንዴ ወንበሩ ላይ

ከተሰየሙ በኋሊ ግን ህዝቡ ለታምራት የሚታያቸው እንደ አሊስፈሊጊ ጩኸት እና እንደ አቧራ ነው።

ቢሯቸው ደረሱ። ቢሮው ውስጥ ያለው ቅንጦት ከውጭ ካለው ድህነት ጋር ሰማይና ምድር ነው። አቶ

ታምራት ወንበራቸው ሊይ ዘና ብለው ተቀመጡ። ስልጣን ጣፋጭ ናት፤ ግን ይህቺን ጣዕም ለማቆየት

ህዝብን ማንቋሸሽ፣ ተቃዋሚን ማሳደድ እና የመንግስትን ሀብት እንደ ግል ንብረት መጠቀም ግዴታ

እንደሆነ ያምናሉ።

ዛሬ ጠዋት አንድ አስቸኳይ ትእዛዝ አስተላለፉ። "ከቢሮዬ ፊት ለፊት ያሉትን ትናንሽ ሱቆች በሙሉ

አንሱ፤ አካባቢውን ያቆሽሹታሉ" አሉ። እነዚያ ሱቆች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦችን

እንደሚያስተዳድሩ ግዴ አልሰጣቸውም። ለእሳቸው ውበትና ስልጣን እንጂ፣ የሰው ልጅ ህይወት

ትርጉም የለውም።

ታምራት ስልኩን አነሱና ወደ ቤታቸው ደወሉ "ዛሬ ማታ ትልቅ ግብዣ አለኝ፣ ከውጭ የመጣ ውድ

ወይን ተዘጋጅቷል?" ብለው ጠየቁ። በችጋርና ረሃብ የተጠበሰው፣ትናትና ከኑሮ ውድነት እንዱሁም

በግፍ ከመገደል እና ሃገር ጥል ከመሰደድ ይታደጉናሌ ብለው የመረጡት ህዝብ ግን ለዳቦ በሚሰለፍበት

ሰዓት፣ታምራት በስልጣን ጣዕም ሰክረዋል። ነገር ግን ይህ ጣፋጭ ስልጣን መራራ ውጤት ይዞ

እንደሚመጣ ገና አላወቁም ነበር፡፡

 

                                    ይቀጥላል.......

ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል አንድ


 

ሳያቋርጡ_ጥረት_ማድረግ (ወጥነት) (consistency

 

                        


በተራራው ጫፍ ላይ የመውጣት ዓላማ ኖሮህ ከተራራው ስር ተቀምጠህ ሽቅብ ወደላይ ስታየው መውጣት ፈፅሞ የሚቻል ላይመስልህ ይችላል፡፡ ነገር ግን ከተቀመጥክበት ተነስተህ የመጀመሪያውን እርምጃ ስታደርግ ከተቀመጥክበት አንድ እርምጃ እየራቅክ ወደ ተራራው ጫፍ አንድ እርምጃ እየቀረብክ ነው ማለት ነው፡፡ 

እርምጃህን ሳታቋርጥ ሽቅብ መጓዝህን ብትቀጥል ከብዙ እርምጃዎች በኋላ ራስህን በተራራው ጫፍ ላይ ልታገኝ ትችላለህ፡፡ እንደት ባለ ሁኔታ ይኼንን አስፈሪ ተራራ እንደወጣህ ከተራራው ጫፍ ላይ ሆነህ ትገረማለህ፡፡

ዛሬ የ2018 ዓ.ም ሐምሌ 3 ነው፡፡ ዓመቱ እያለቀ ነው። በዚህ ዓመት አሳካዋለው ብለህ ያቀድከውን ዕቅድ ገምግመህ ለቀጣዩ የዓመት ዕቅድህን አንድ ብለህ ማቀድ እና መዘጋጀት ትችላለህ፡፡ በዚህ ውሳኔህ ከፀናህና ሳታቋርጥ "consistently" ዕቅድህን መተግበር ከቻልክ የዓመቱን ዕቅድህን ከማሳካት ወደ ኋላ አትመለስም፡፡ 

የዛሬው ጥረትህ ብቻዋን ከምንም የማትቆጠር ትንሽዬ ተግባር ሆና ልታገኛት ትችላለህ፡፡ ነገር ግን የየቀኑ ትንንሽ ተግባራት ድምር ውጤት ትልቅ ተግባር ይሆናል። ስለዚህ በዓመቱ መጨረሻ ላይ ለማሳካት ስላሰብከው ትልቅ ውጤት ማሰብህን ለጊዜው አቁመህ የዛሬ ተግባርህን ለራስህ #ታማኝ ሆነህ መተግበር ጀምር፡፡ 

ቀስ በቀስ ወደ ስኬትህ እየቀረብክ አሁን ካለህበት እየራቅክ እንደሚትሄድ አውቀህ ዛሬውኑ ጀምር፣ ነገም ቀጥልበት፣ ከነገ ወዲያም አታቋርጥ፡፡ ከሳምንት ወደ ሳምንት፣ ከወር ወደ ወር ሳታቋርጥ ጥረት በማድረግ ከተነሳህበት መነሻ እየራቅክ ወደ መዳረሻህ እየቀረብክ መምጣትህ የማይቀር ነው፡፡ 

እግዚአብሔር በነገር ሁሉ መከናወንን ይስጠን!

ስልጣንና ጣዕሙ

                                                       



"ስልጣንና ጣዕሙ" የሰው ልጅ በስልጣን ጥም፣ በክህደትና በእውነት መካከሌ የሚያደርገውን ውስብስብ

ትግል የሚዲስስ ታሪክ ነው። ታሪኩ የሚጀምረው ከከፍታ ማማ ላይ ሆኖ ዓለምን በሚገዛው አቶ

ታምራት ቢሆንም፣ በውስጡ ግን ለሃያ ዓመታት ተቀብሮ የቆየ የጨለማ ምስጢር ይዟል።

በዚህ መጽሏፍ ውስጥ፣ ስልጣን እንደ ማር የጣፈጠቻቸው ባለስልጣናት በክህደት የገነቡት ህንፃ

በእውነት ማዕበል ሲናድ እንመለከታለን። ያለፈ ታሪክ ምንም ያህል ቢቀበር፣ ትክክለኛ ሰዓቱን ጠብቆ

ዳግም መውጣቱ የማይቀር መሆኑን ታሪኩ በዝርዝር ያሳያል። "ቀይ ብዕር" የተባለው ምስጢራዊ ገፀ-

ባህሪ ደግሞ፣ የፍትህ መዛግብት በዝምታ ቢፃፉም መጨረሻቸው ግን ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን

የሚያሳይ የጽናት ተምሳሌት ነው።

የጽሐፉ መልዕክት፡ 

 የሥነ-ምግባር ትምህርት መስጠት

 የፍትህና የእውነትን ዋጋ ማጉላት

 የሰው ልጅን ውስጣዊ ማንነት መመርመር

 አንባቢን ማዝናናትና ማሳተፍ


ከክፍል አንድ እስከ ክፍል አስራ አራት 



popular post

Result Portal