ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል አንድ
አቶ ታምራት ጥቁር መስታወት ባለው ዘመናዊ መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመስኮት ወደ ውጭ
ይመለከታለ። መንገደ በሰዎች ብዛት ተጨናንቋል። ፀሃዩ የበረታበትና ላባቸውን በክንዳቸው የሚጠረጉ
ሰራተኞች፣ ቅርጫት የተሸከሙ እናቶች፣ እና አቧራ የለበሱ ህፃናት በመንገደ ግራና ቀኝ
ይተማመታሉ።
ታምራት ፊታቸውን አኮሳተሩ። "ይህ ሁለ ህዝብ የት ነው የሚሄደው? መንገደን እንዱህ
የሚያጨናንቁት ስራ ስለሌላቸው ነው" አለ። አብሯቸው የነበረው የግሌ ረዲታቸው። ዴምፃቸው ውስጥ
ከፍተኛ ንቀት ይንጸባረቃል። ከጥቂት አመታት በፊት ምርጫ ሲቃረብ፣ በእነዚሁ ሰዎች ሰፈር እየተገኙ
"እኔ የእናንተ ሌጅ ነኝ፣ ለውጥ አመጣለሁ" እያለ ጎንበስ ብልው ሲማጸኑ የነበሩት ታምራት፣ ዛሬ
በህዝቡ መሀል ማለፍ እንደ መርገም ቆጥረውታል።
ለእሳቸው ህዝብ ማለት ስልጣን ሊይ እስኪወጡ የሚጠቀሙበት "ቁጥር" ብቻ ነው። አንዴ ወንበሩ ላይ
ከተሰየሙ በኋሊ ግን ህዝቡ ለታምራት የሚታያቸው እንደ አሊስፈሊጊ ጩኸት እና እንደ አቧራ ነው።
ቢሯቸው ደረሱ። ቢሮው ውስጥ ያለው ቅንጦት ከውጭ ካለው ድህነት ጋር ሰማይና ምድር ነው። አቶ
ታምራት ወንበራቸው ሊይ ዘና ብለው ተቀመጡ። ስልጣን ጣፋጭ ናት፤ ግን ይህቺን ጣዕም ለማቆየት
ህዝብን ማንቋሸሽ፣ ተቃዋሚን ማሳደድ እና የመንግስትን ሀብት እንደ ግል ንብረት መጠቀም ግዴታ
እንደሆነ ያምናሉ።
ዛሬ ጠዋት አንድ አስቸኳይ ትእዛዝ አስተላለፉ። "ከቢሮዬ ፊት ለፊት ያሉትን ትናንሽ ሱቆች በሙሉ
አንሱ፤ አካባቢውን ያቆሽሹታሉ" አሉ። እነዚያ ሱቆች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦችን
እንደሚያስተዳድሩ ግዴ አልሰጣቸውም። ለእሳቸው ውበትና ስልጣን እንጂ፣ የሰው ልጅ ህይወት
ትርጉም የለውም።
ታምራት ስልኩን አነሱና ወደ ቤታቸው ደወሉ "ዛሬ ማታ ትልቅ ግብዣ አለኝ፣ ከውጭ የመጣ ውድ
ወይን ተዘጋጅቷል?" ብለው ጠየቁ። በችጋርና ረሃብ የተጠበሰው፣ትናትና ከኑሮ ውድነት እንዱሁም
በግፍ ከመገደል እና ሃገር ጥል ከመሰደድ ይታደጉናሌ ብለው የመረጡት ህዝብ ግን ለዳቦ በሚሰለፍበት
ሰዓት፣ታምራት በስልጣን ጣዕም ሰክረዋል። ነገር ግን ይህ ጣፋጭ ስልጣን መራራ ውጤት ይዞ
እንደሚመጣ ገና አላወቁም ነበር፡፡
ይቀጥላል.......