ታማኛለች ቀርፋፋ ነው እያለች ፤ አላወቀችም ከብዙ ቀን ጥርቅም በኋላ መራመድ እንደሆነልኝ ፤ ተዓምር ሆኖ ባርቆብኝ ፣ ደክሞኝ እየተራመድኩ እንደሆነ ብታውቅ መንቀራፈፌ ሳይሆን መራመዴ ትንግርት ይሆንባት ነበር!
ደግሞ አሮጌ ጨርቅ ማጥለቄ ደህይቼ መስሏታል ፤ ከጎዳና ላይ ተነስቼ ከብጭቅጫቂ ጨርቅ ወደ አሮጌ ጨርቅ ማደጌን ብታውቅ ደህይቼ ሳይሆን እያለፈለኝ መሆኔን ትገነዘብ ነበር።
ትክ ብዬ ማየቴ ድፍረት ነው የመሰላት ፤ አንገቴን ደፍቼ መኖሬን ብታውቅ ቀና ከማለት አድጌ በልበ-ሙሉነት ማየቴ ድፍረት ሳይሆን ልበ-ሙሉነቴ አድጎ እንደሆነ ትመሰክርልኝ ነበር ።
እግረመንገዱን የመጣ መዛኝ እየመዘነ ነው የሚያስቀን !
ችላ ስትለኝ ችላ ማለቷን ከቁብ ያለመቁጠር ንቀት ነው የመሰላት ግን አይደለም ፤
የስህተታችን ጅማሬ በሁሉም ሰው ተቀባይነት ለማግኘት መዳከር ነው የሚለው ጥበብ ገብቶኝ እንጂ ።
እኔ ግን ትግሌ ከራሴ ትናንት ጋ ነው!!!
@keye_ber

No comments:
Post a Comment