የማይታየው እጅ
አቶ ታምራት በቢሯቸው መስኮት በኩል የሚያዩትን የከተማዋን ውበት ጥለው ወደ ጠረጴዛቸው
ተመለሱ። በዝግጅት ላይ ያለው የዛሬ ምሽቱ ግብዣ ከፍ ያለ ክብር እንደሚሰጣቸው ያውቃለ። ልክ
ወንበራቸው ሊይ እንዯተቀመጡ ግን ባሌተሇመዯ መሌኩ በቢጫ ፖስታ የታሸገ ዯብዲቤ በጠረጴዛቸው
መሃል ተቀምጦ አዩ።
"ይህንን ማን አምጥቶ እዚህ አስቀመጠው?" ብለው ጮኹ። ረዳታቸው እየተንቀጠቀጠ ገባ። "ጌታዬ...
እኔ አላየሁም፣ ማንም አልገባም" አላቸው።
ታምራት ደብዳቤውን በቁጣ ቀደዱ። ውስጥ ያለው ግን ጽሐፍ ሳይሆን አንዴ የቆየ ፎቶ ነበር።
ፎቶው የዛሬ ሃያ አመት በፊት የተነሳ ነው። ታምራት እና ሶስት ጓደኞቻቸው ምሽግ በሆነ ሰፈር፣
ፊታቸው ላይ ስጋት እየታየ አንድ ትልቅ ቦርሳ ይዘው ይታያለ። በፎቶው ጀርባ ላይ እንዲህ የሚል
ጽሐፍ በደም ቀለም የሚመስል ቀይ ቀለም ተጽፏል፦
"ስሌጣን ላይ ስትወጣ የረገጥከው መሰላል፣ መውረጃህ ሊይ እሾህ ሆኖ ይጠብቅሃል። ያንን ቦርሳና
በውስጡ የነበረውን ሚስጥር ረሳኸው ታምሬ?"
ታምራት ትንፋሻቸው ተቆረጠ። "ታምሬ" ብሎ የሚጠራቸው ያ የዴሮ ጓደኛቸው መሞቱን እርግጠኛ
ነበሩ። እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስልኩን አነሱ። የደህንነት ክፍሉን በመጥራት አስበው ግን ተዉት። ይህ
ሚስጥር ከወጣ ስልጣናቸው ብቻ ሳይሆን ህይወታቸውም እንደሚያከትም ያውቃሉ።
በዚህ መሃል የቢሮው ስሌክ አቃጨለ። "ሄሎ" አሉ።
ዴምፁ ቀዝቃዛ ነው... "ጣዕሙ እንዴት ነው ታምራት? ገና መራራው ክፍሌ አልደረሰም። ዛሬ ምሽት
ግብዣህ ላይ እገኝ ይሆናል" ብሎ ተዘጋ።
ታምራት ቢሯቸው ውስጥ ብቻቸውን ሆነው ላባቸው ይፈስ ጀመር። ያንቋሸሹት ህዝብ ሳይሆን፣
የቀበሩት ታሪክ አፋቸውን ከፍቶ ሊውጣቸው እንደመጣ ተገነዘቡ......
ይቀጥላል.......
No comments:
Post a Comment