Showing posts with label የቀይ ብዕር ዲያሪ. Show all posts
Showing posts with label የቀይ ብዕር ዲያሪ. Show all posts

ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል ሦስት

                        

                    የጥርጣሬ ጥላ 

የቢሮው ስልክ ተዘጋ። ታምራት ግን አሁንም ስልኩን እንደያዙት በዴንጋጤ እና ግራ በመጋባት

ቆመዋል። ያ ዴምፅ... ያ ዴምፅ ጆሯቸው ውስጥ እያስተጋባ ነው። "ታምሬ" የሚሇውን ቃሌ

የሚጠቀመው አንዴ ሰው ብቻ ነበር። ግን እሱ ከሃያ ዓመት በፊት በነበረው በዚያ አስከፊ ምሽት

መሞቱን በዓይናቸው አይተዋል። ታዱያ ዛሬ ከመቃብር የወጣው ማን ነው?

ረዳታቸው በሩን ከፍቶ ገባ። "ጌታዬ፣ ለምሽቱ ግብዣ የሚለበሰው ልብስ ተዘጋጅቷል። እንዱሁም የክብር

እንግድቹ ዝርዝርም..."

"ውጣ!" ብለው ጮኹ ታምራት። ረዳቱ ደንግጦ ወደኋላ አፈገፈገ። ታምራት አሁን ማንም ሰው

እንዲቀርባቸው አይፈልጉም። በቢሮው ውስጥ ያለት ዘመናዊ ካሜራዎች እንኳ እሳቸውን የሚሰልሉ

መሰላቸው። ያ ቢጫ ፖስታ ውስጥ የነበረው ፎቶ የያዘው ሚስጥር ቀላል አይደለም። በፎቶው ላይ

ካለት አራት ሰዎች መካከሌ ዛሬ በሕይወት ያሉት እሳቸውና ላላኛው ጓደኛቸው አቶ ክፍሌ ብቻ

ናቸው።

ክፍሌን ለማግኘት ወዲያውኑ ስሌካቸውን አነሱና ደወለ። ክፍሌ አሁን የትልቅ ዴርጅት ባለቤት

ቢሆንም፣ በታምራት  ስልጣን ጥላ ስር የሚኖር ሰው ነው።

"ክፍሌ፣ ደብዳቤ ደርሶሃል?" አለ ታምራት። ድምፃቸው ይንቀጠቀጣል።

"ምን አይነት ደብዳቤ ታምሬ? ምንም አልደረሰኝም" አላቸው ክፍሌ። "ምነው ደነገጥክ? ዛሬ ምሽት

ታላቁን ድልህን የምታከብርበት ግብዣ አይደለም ወይ?"

"ክፍሌ... ፎቶው ተመልሶ መጥቷል። ያ የጫካው ፎቶ!"

በሌላኛው ወገን ረጅም ዝምታ ሰፈነ። የክፍሌ ትንፋሽ ሲቆራረጥ ይሰማል። "ማን? ማን ነው የላከው? 

እሱ... እሱማ ሞቷል አይደል?"

"አላውቅም። ግን ዛሬ ምሽት ግብዣው ላይ እመጣለሁ ብሎኛል። ክፍሌ፣ ይህ ሚስጥር ከወጣ

ሁለታችንም እናልቃለን። ያ ሁለ ህዝብ ፊት የምናሳየው ክብር በአንድ ቀን አመድ ይሆናል" አለ።

ታምራት ስሌኩን ዘግተው ወደ መስኮቱ ተመለሱ። አሁን መስኮቱ ላይ የሚታያቸው ያንቋሸሹትና

የናቁት ህዝብ አይደለም። በየጥላው ስር ሆነው የሚከታተሏቸው ጠላቶች ናቸው። ስልጣን ጣፋጭ

ነበረች፤ አሁን ግን ጣዕሟ ወደ መራራነት እየተቀየረ ነው።

ምሽቱ ደረሰ። የከተማው ባለስልጣናትና ባለሀብቶች በታምራት ግቢ ውስጥ ተሰብስበዋል። ታምራት

በግዳጅ ይመስል እየሳቁ እንግዶችን ይቀበላሉ። ነገር ግን ዓይኖቻቸው የሚፈልጉት አንድን ሰው ነው። በሕዝቡ

መሀል ሆኖ በንቀት የሚመለከታቸውን፣ ያንን የድሮ ሚስጥር የያዘውን ሰው።

በዚህ መሀል አንድ ግዙፍ ሰው ወደ ታምራት ቀረበ። እጁን ለሰላምታ ዘረጋ። ታምራት ሰውየውን

ሲያዩት የያዙት የወይን ብርጭቆ ከእጃቸው አምልጦ መሬት ላይ ተከሰከሰ።


                                                                 ይቀጥላል....

ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል ሁለት

                              የማይታየው እጅ 


አቶ ታምራት በቢሯቸው መስኮት በኩል የሚያዩትን የከተማዋን ውበት ጥለው ወደ ጠረጴዛቸው

ተመለሱ። በዝግጅት ላይ ያለው የዛሬ ምሽቱ ግብዣ ከፍ ያለ ክብር እንደሚሰጣቸው ያውቃለ። ልክ

ወንበራቸው ሊይ እንዯተቀመጡ ግን ባሌተሇመዯ መሌኩ በቢጫ ፖስታ የታሸገ ዯብዲቤ በጠረጴዛቸው

መሃል ተቀምጦ አዩ።

"ይህንን ማን አምጥቶ እዚህ አስቀመጠው?" ብለው ጮኹ። ረዳታቸው እየተንቀጠቀጠ ገባ። "ጌታዬ... 

እኔ አላየሁም፣ ማንም አልገባም" አላቸው።

ታምራት ደብዳቤውን በቁጣ ቀደዱ። ውስጥ ያለው ግን ጽሐፍ ሳይሆን አንዴ የቆየ ፎቶ ነበር።

ፎቶው የዛሬ ሃያ አመት በፊት የተነሳ ነው። ታምራት እና ሶስት ጓደኞቻቸው ምሽግ በሆነ ሰፈር፣

ፊታቸው ላይ ስጋት እየታየ አንድ ትልቅ ቦርሳ ይዘው ይታያለ። በፎቶው ጀርባ ላይ እንዲህ የሚል

ጽሐፍ በደም ቀለም የሚመስል ቀይ ቀለም ተጽፏል፦

"ስሌጣን ላይ ስትወጣ የረገጥከው መሰላል፣ መውረጃህ ሊይ እሾህ ሆኖ ይጠብቅሃል። ያንን ቦርሳና

በውስጡ የነበረውን ሚስጥር ረሳኸው ታምሬ?"

ታምራት ትንፋሻቸው ተቆረጠ። "ታምሬ" ብሎ የሚጠራቸው ያ የዴሮ ጓደኛቸው መሞቱን እርግጠኛ

ነበሩ። እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስልኩን አነሱ። የደህንነት ክፍሉን በመጥራት አስበው ግን ተዉት። ይህ

ሚስጥር ከወጣ ስልጣናቸው ብቻ ሳይሆን ህይወታቸውም እንደሚያከትም ያውቃሉ።

በዚህ መሃል የቢሮው ስሌክ አቃጨለ። "ሄሎ" አሉ።

ዴምፁ ቀዝቃዛ ነው... "ጣዕሙ እንዴት ነው ታምራት? ገና መራራው ክፍሌ አልደረሰም። ዛሬ ምሽት

ግብዣህ ላይ እገኝ ይሆናል" ብሎ ተዘጋ።

ታምራት ቢሯቸው ውስጥ ብቻቸውን ሆነው ላባቸው ይፈስ ጀመር። ያንቋሸሹት ህዝብ ሳይሆን፣

የቀበሩት ታሪክ አፋቸውን ከፍቶ ሊውጣቸው እንደመጣ ተገነዘቡ......

                                  ይቀጥላል.......

 


ታማኛለች ቀርፋፋ ነው እያለች ፤ አላወቀችም ከብዙ ቀን ጥርቅም በኋላ መራመድ እንደሆነልኝ  ፤ ተዓምር ሆኖ ባርቆብኝ ፣ ደክሞኝ እየተራመድኩ እንደሆነ ብታውቅ መንቀራፈፌ ሳይሆን መራመዴ ትንግርት ይሆንባት ነበር!

ደግሞ  አሮጌ ጨርቅ ማጥለቄ  ደህይቼ  መስሏታል ፤ ከጎዳና ላይ ተነስቼ  ከብጭቅጫቂ ጨርቅ ወደ አሮጌ ጨርቅ ማደጌን ብታውቅ ደህይቼ ሳይሆን እያለፈለኝ መሆኔን ትገነዘብ ነበር።

ትክ ብዬ ማየቴ  ድፍረት ነው የመሰላት ፤ አንገቴን ደፍቼ መኖሬን ብታውቅ ቀና ከማለት አድጌ በልበ-ሙሉነት ማየቴ ድፍረት ሳይሆን ልበ-ሙሉነቴ አድጎ እንደሆነ ትመሰክርልኝ ነበር ። 

እግረመንገዱን የመጣ መዛኝ እየመዘነ ነው የሚያስቀን !

ችላ ስትለኝ ችላ ማለቷን ከቁብ ያለመቁጠር  ንቀት  ነው የመሰላት  ግን አይደለም ፤
የስህተታችን ጅማሬ በሁሉም ሰው ተቀባይነት ለማግኘት መዳከር ነው የሚለው ጥበብ ገብቶኝ እንጂ ። 

እኔ ግን ትግሌ ከራሴ ትናንት ጋ ነው!!!
              
@keye_ber

ስልጣንና ጣዕሙ


         ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል አንድ 

አቶ ታምራት ጥቁር መስታወት ባለው ዘመናዊ መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመስኮት ወደ ውጭ

ይመለከታለ። መንገደ በሰዎች ብዛት ተጨናንቋል። ፀሃዩ የበረታበትና ላባቸውን በክንዳቸው የሚጠረጉ

ሰራተኞች፣ ቅርጫት የተሸከሙ እናቶች፣ እና አቧራ የለበሱ ህፃናት በመንገደ ግራና ቀኝ

ይተማመታሉ።

ታምራት ፊታቸውን አኮሳተሩ። "ይህ ሁለ ህዝብ የት ነው የሚሄደው? መንገደን እንዱህ

የሚያጨናንቁት ስራ ስለሌላቸው ነው" አለ። አብሯቸው የነበረው የግሌ ረዲታቸው። ዴምፃቸው ውስጥ

ከፍተኛ ንቀት ይንጸባረቃል። ከጥቂት አመታት በፊት ምርጫ ሲቃረብ፣ በእነዚሁ ሰዎች ሰፈር እየተገኙ

"እኔ የእናንተ ሌጅ ነኝ፣ ለውጥ አመጣለሁ" እያለ ጎንበስ ብልው ሲማጸኑ የነበሩት ታምራት፣ ዛሬ

በህዝቡ መሀል ማለፍ እንደ መርገም ቆጥረውታል።

ለእሳቸው ህዝብ ማለት ስልጣን ሊይ እስኪወጡ የሚጠቀሙበት "ቁጥር" ብቻ ነው። አንዴ ወንበሩ ላይ

ከተሰየሙ በኋሊ ግን ህዝቡ ለታምራት የሚታያቸው እንደ አሊስፈሊጊ ጩኸት እና እንደ አቧራ ነው።

ቢሯቸው ደረሱ። ቢሮው ውስጥ ያለው ቅንጦት ከውጭ ካለው ድህነት ጋር ሰማይና ምድር ነው። አቶ

ታምራት ወንበራቸው ሊይ ዘና ብለው ተቀመጡ። ስልጣን ጣፋጭ ናት፤ ግን ይህቺን ጣዕም ለማቆየት

ህዝብን ማንቋሸሽ፣ ተቃዋሚን ማሳደድ እና የመንግስትን ሀብት እንደ ግል ንብረት መጠቀም ግዴታ

እንደሆነ ያምናሉ።

ዛሬ ጠዋት አንድ አስቸኳይ ትእዛዝ አስተላለፉ። "ከቢሮዬ ፊት ለፊት ያሉትን ትናንሽ ሱቆች በሙሉ

አንሱ፤ አካባቢውን ያቆሽሹታሉ" አሉ። እነዚያ ሱቆች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦችን

እንደሚያስተዳድሩ ግዴ አልሰጣቸውም። ለእሳቸው ውበትና ስልጣን እንጂ፣ የሰው ልጅ ህይወት

ትርጉም የለውም።

ታምራት ስልኩን አነሱና ወደ ቤታቸው ደወሉ "ዛሬ ማታ ትልቅ ግብዣ አለኝ፣ ከውጭ የመጣ ውድ

ወይን ተዘጋጅቷል?" ብለው ጠየቁ። በችጋርና ረሃብ የተጠበሰው፣ትናትና ከኑሮ ውድነት እንዱሁም

በግፍ ከመገደል እና ሃገር ጥል ከመሰደድ ይታደጉናሌ ብለው የመረጡት ህዝብ ግን ለዳቦ በሚሰለፍበት

ሰዓት፣ታምራት በስልጣን ጣዕም ሰክረዋል። ነገር ግን ይህ ጣፋጭ ስልጣን መራራ ውጤት ይዞ

እንደሚመጣ ገና አላወቁም ነበር፡፡

 

                                    ይቀጥላል.......

ስልጣንና ጣዕሙ ክፍል አንድ


 

ስልጣንና ጣዕሙ

                                                       



"ስልጣንና ጣዕሙ" የሰው ልጅ በስልጣን ጥም፣ በክህደትና በእውነት መካከሌ የሚያደርገውን ውስብስብ

ትግል የሚዲስስ ታሪክ ነው። ታሪኩ የሚጀምረው ከከፍታ ማማ ላይ ሆኖ ዓለምን በሚገዛው አቶ

ታምራት ቢሆንም፣ በውስጡ ግን ለሃያ ዓመታት ተቀብሮ የቆየ የጨለማ ምስጢር ይዟል።

በዚህ መጽሏፍ ውስጥ፣ ስልጣን እንደ ማር የጣፈጠቻቸው ባለስልጣናት በክህደት የገነቡት ህንፃ

በእውነት ማዕበል ሲናድ እንመለከታለን። ያለፈ ታሪክ ምንም ያህል ቢቀበር፣ ትክክለኛ ሰዓቱን ጠብቆ

ዳግም መውጣቱ የማይቀር መሆኑን ታሪኩ በዝርዝር ያሳያል። "ቀይ ብዕር" የተባለው ምስጢራዊ ገፀ-

ባህሪ ደግሞ፣ የፍትህ መዛግብት በዝምታ ቢፃፉም መጨረሻቸው ግን ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን

የሚያሳይ የጽናት ተምሳሌት ነው።

የጽሐፉ መልዕክት፡ 

 የሥነ-ምግባር ትምህርት መስጠት

 የፍትህና የእውነትን ዋጋ ማጉላት

 የሰው ልጅን ውስጣዊ ማንነት መመርመር

 አንባቢን ማዝናናትና ማሳተፍ


ከክፍል አንድ እስከ ክፍል አስራ አራት 



 


                      የንስር ሕይወት ትምህርት

ይህን ያውቁ ኖሯል?  ከሁሉም ወፎች መካከል ንስርን ለመረበሽ የሚደፍር ቁራ ብቻ ነው። ንስር ይኼን ስታይ 👉 ጥበብ ትጠቀማለች። ቁራውን ተመልሳ ለማጥቃት በፍፁም አትጨነቅም፤ ይልቁንም ስለ ራሷ ጥንካሬ እና ስኬት ጥልቅ እውነት ታሳየናለች።


ቁራ ያለ አንዳች ሃፍረት በንስር ጀርባ ላይ አርፋ ሰላም ትነሳታለች፣ የንስርን ላባ ትነጫለች፣ ትረብሻለች፣ ታናድዳታለች፣ ሳታቋርጥ እረፍት ትነሳታለች። 

ነገር ግን ንስር ጉልበቷን በቁራ ንዝነዛ አታባክንም። አላስፈላጊ ትግል አታደርግም። የበቀል እርምጃም አትወስድም።  ነገር ግን ንስር አንድ ውሳኔ ትወስናለች፤ ሙሉ ኃይሏን ተጠቅማ ወደ ላይ ወደ ከፍታ ትወጣለች።


ከፍታ ብቻ ነው ከቁራ ጋር የገጠማትን ችግር የሚፈታው። ንስር ወደ ላይ ከፍ እያለች በሄደች ቁጥር ቁራ አየር እያጠራት፣ መተንፈስ እያቃታት፣ መድከም ትጀምራለች። በመጨረሻም ንስሯን ትታ ለመውደቅ ትገደዳለች። እውነተኛ ድል የሚገኘው ከፍ ብሎ በመነሳት ውስጥ እንጂ ከሚነዘንዙህ ጋር ግብግብ በመፍጠር አይደለም፤ ለአሉባልተኞች መልስ በመስጠትም አይደለም። ስላንተ ስያወሩ ውለው ቢያድሩ እንኳን እንዳላየህ፣ እንዳልሰማህ ሆነህ ዝም በላቸው። ንስሯ ተዋግታ አላሸነፈችም። በቀላሉ ከፍ በማለቷ ብቻ ቁራ ራሱን ሊያጠፋ ችሏል። 


ይህንን እወቅ፦ ሌሎች ይናቁህ፣ ይናገሩ፣ ይውቀሱህ፣ ይተቹህ፣ ይሳለቁ።  አንተ ግን እነሱን ለመገዳደር ስባል ጊዜ አታባክን፤ የፈለጉትን ያድርጉ። ይልቁን ለማደግ ፣ ለመራመድ ፣ አዲስ ከፍታ ላይ ለመድረስ ተንቀሳቀስ። 


ምክንያቱም እውነታው እዚህ ጋር ነው፡- ሰዎች አንተ የደረስክበት ከፍታ  ላይ መድረስ አቅቷቸው ይተዉሃል። ምንም ሳይሆን ከፍታህ ብቻ ጩኸታቸውን ጸጥ ያደርጋል። ወደ ታች ለመነታረክ ዝቅ አትበል፤ ወደ ላይ ማደግህን ቀጥል!    

popular post

Result Portal